ፍቺ
ለይቶ ማቆየት ማለት አንድ በበሽታ ከተጠቃ ሰው ጋር ተጋላጭነት የነበረው ሰውን ከሌለው (ከጤነኛው) መለየት ነው፡፡ ብዘውን ጊዜ ሰዎች በቫይረሱ መጠቃታቸውን አያውቁትም (ለምሳሌ ሲጓዙ ወይም ከህዝብ ጋር በጋራ ሲሆኑ) ወይም በበሽታው መጠቃታቸውን ሳያውቁና ምልክት ሳይታይባቸው በሽታው ይኖርባቸዋል፡፡
ለብቻ ማግለል ማለት አንድን ታማሚ ከጤነኛው ሰው መነጠል ነው፡፡ ራሳቸውን እያገለሉ ያሉ ሰዎች ቤት ውስጥ መቆየት ይኖርባቸዋል፡፡እነኚህ ሰዎች ቤት ውስጥ በሚቆዩበት ጊዜ በተቻለ መጠን በራሳቸው በሆነ አንድ ክፍል ውስጥ መሆን ይኖርባቸዋል ቢቻል ሽንት ቤትም ጭምር ቢለይ ይመረጣል፡፡
ምንጭ፡ ከበሽታ መከላከልና ቁጥጥር ባለስልጣን